ለጤና ባለሙያዎች ለCOVID-19 ወረርሽ ለመከላከል የቀረበ ጥሪ
በዓለም ላይ በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ሀገራችን ውስጥ መከሰቱም ይታዎቃል፡፡ በመንግሥትና በበጎ ፍቃደኛ ሰዎች ወረርሽኙን ለመቆጣጠጠር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ሲሆን ወደፊት የወረርሽኙ ሁኔታ እየከፋ ከመጣ በርካታ የበጎ ፍቃድ ባለሙያዎችን ማሰማራት ስለሚጠይቅ፤
- በጤና ሙያ ተመርቃችሁ ወደ ሥራ ያልተሰማራችሁ
- መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት የምትሰሩ የጤና ባለሙያዎች
- በጡረታና በተለያዩ ምክንያቶች ከሥራ የተገለላችሁ የጤና ባለሙዎች (ለመደበኛ አገልግሎት)
- የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን
- የጤና ተማሪዎች (በመንግስትና በግል)
ከመጋቢት 24 ቀን 2012 ጀምሮ ከዚህ በታች በተገለፀው የጤና ሚኒስቴር ድረ-ገፅ እንድትመዘገቡ ሀገራዊ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ http://www.moh.gov.et/ejcc/am/node/201
http://www.moh.gov.et/ejcc/am/node/201?fbclid=IwAR2oj9Jhye8a7qU6LRHXEjdX...
ጤና ሚኒስቴር